ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል

image

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የበላይ ጠባቂ `


1.የግል ማኅደር 

 የትውልድ ሥፍራ - በቀድሞ አጠራሩ ወለጋ ጠቅላይ ግዛት ጊምቢ ከተማ 

 አድራሻ - አዲስ አበባ ከተማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክጠቅላይ ቤተ ክህነት 

 ስልክ ቁጥር 

+251911132481 

ኢሜይል

archbishophenok@gmail.com

info@archbishophenok.org

2.መንፈሳዊ ትምህርት 

 በቂልጡ ካራ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የአብነት ትምህርት ቤት መሪጌታ አእምሮ ከሚባሉ መምህርንባብና ዳዊት ተምረዋል 

 በደብረ ሊባኖስ ገዳም ከየኔታ ቀጸላ ከውዳሴ ማርያም ዜማ እስከ ምዕራፍ ተምረዋል 

 በሞጣ አካባቢ በመዘዋወር ከየኔታ ኪነጥበብ የቅኔ ትምህርትን ተምረዋል  

  በዚያው በሞጣ ከየኔታ አእመረ ቅዳሴ ተምረዋል 

 በመቀጠልም ወደ ርዕሰ አድባራት መርጦለማርያም ገዳም በመሄድ ከየኔታ ሀብቴ ለአምስት አመታትየቅኔ ትምህርታቸውን በመከታተል አጠናቅቀዋል  

 ከየኔታ ይሁን ዝማሬ መዋሥዕት በመማር አጠናቅቀዋል። 

 ከየኔታ ኅሩይ አርባዕቱን ወንጌላት ተምረዋል፡፡ 

3.ዘመናዊ ትምህርት 

 አሶ ትምህርት ቤት እና አድቬንቲስት ትምህርት ቤቶች እና በጊምቢ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችትምህርታቸውን ተከታትለዋል 

 1994 . ጀምሮ በነቀምቴ መስከረም ሁለተሰ ትምህርት ቤት በመግባት የመሰናዶትምህርታቸውን ተከታትለዋል 

 ከአዲስ አበባ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ በዲፕሎማ ተመርቀዋል። 

 የባችለር ዲያግሪያቸውን በንግድ አስተዳደር ከቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል። 

 ጀርመን ሀገር ከሚገኘው ኢንተርናሽናል ቢዝነስ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት በፕሮጀክት ማኔጅመንትከፍተኛ ዲፕሎማ አግኝተዋል 

  በሀገረ ጀርመን ከሚገኘው አይ  ኤም አይ በፕሮጀክት ማኔጅመንት የማስተርስ ዲግሪአግኝተዋል። 

 ከአውሮፖ ኢንስቲትዩት ኦፍ ሊደርሺፕ ኤንድ ማኔጅመንት በኢንተርናሽናል ሪሌሽን ሰርተፊኬትአግኝተዋል። 

4. ክህነት 

 ነሐሴ 22 ቀን 1997 . የምዕራብ ወለጋ ኤጲስ ቆጶስ በመሆን በብፁዕ ወቅዱስ / አቡነጳውሎስ አንብሮተ ዕድ ተሹመዋል። 

 1990 ዓመተ ምህረት ከብፁዕ አቡነ ዘካርያስ የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅስናማዕረግን ተቀብለዋል። 

 በመርጡለማርያም ገዳም ምንኵስናን ከመምህር አባ /ኢየሱስ 1985 . ተቀብለዋል። 

 1975 . ከብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ ማዕረገ ዲቁናን ተቀብለዋል፡፡ 

5. አገልግሎት 

 በጸሎተ ማኅበር፣ የልማት ሥራ በመሥራትና አቅመ ደካሞችን በመርዳት የመርጦለማርያም ገዳምንአገልግለዋል፡፡ 

 ከዚያ በመቀጠል በጎጃም ክፍለ ሀገር በተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር በቅዳሴና በማኅሌትሲያገለግሉ ቆይተዋል። 

 1994 . ጀምሮ በብፁዕ አቡነ ኤልያስ የወለጋ ሀገረ ስብከት መልካም ፈቃድ የነቀምቴ ገነተኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ዋና አስተዳዳሪ በመሆን እስከ 1997 . ድረስ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንንበቅንነትና በታማኝነት ሲያገለግሉ ቆይተዋል። 

 ከነሐሴ 1997 - 2011 . የምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ 

 1998 - 2011 . በተደራቢነት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ 

 2001 . በምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሥር የነበረው የቄለም ወለጋ ሀገረ ስብከት ራሱን ችሎእንዲቋቋም በማድረግ እስከ 2011 . ድረስ በተደራቢነት የዚሁ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ 

 2008 - 2011 . የአውስትራሊያ እና የኒውዝላንድ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ 

 2011 - ጥቅምት 2015 . የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ 

 ከጥቅምት 2015 - ግንቦት 2017 ድረስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

 ከግንቦት 2017 . ጀምሮ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመሆን እያገለገሉይገኛሉ።

6. በብፁዕነታቸው የተሰሩ እና እየተሰሩ ያሉ ዐበይት ተግባራት 

 ብፁዕነታቸው ጥቅምት 1998 . ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስባቀረቡት ጥያቄ መሠረት የኦሮምኛ ቅዳሴ ትርጉም እንዲዘጋጅና ለምዕመናኑ ተደራሽ እንዲሆንበማድረግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ከማድረግም በላይ በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያንበቋንቋቸው እንዲማሩ እና የኦሮምኛ ቅዳሴ ትርጉም ተዘጋጅቶ ለአገልግሎት እንዲበቃ አድርገዋል። 

 የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሀገረ ስብከት በክልሉ የሚገኙ ብሔረሰቦች በቋንቋቸው እንዲያገለግሉከማበረታታትም በላይ በርካቶች መሠረታዊ እና ከፍተኛ የቲዮሎጂ ትምህርት በመማር የአካባቢውንሕብረተሰብ ማገልገል እንዲችሉ በማድረግ በከፍተኛ ሁኔታ የኖላዊነት ግዴታቸውን ሲወጡቆይተዋል። 

 የቄለም ወለጋ ምዕመናን መንፈሳዊ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አገልግሎቶች በቅርበት እንዲያገኙለማድረግ ሀገረ ስብከት እንዲደራጅ በማድረግ አስተዋፅኦ አድርገዋል። 

 በአውስትራሊያና የኒውዝላንድ አህጉረ ስብከት ከአኃት አብያተ ክርስቲያናት ጋር ያለው ግንኙነትእንዲጠናከር በማድረግና በውጭ የተወለዱ ሕጻናት በምግባርና በሃይማኖት እንዲታነፁ ለማድረግከፍተኛ ሥራን ሲሰሩ ቆይተዋል። 

 በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በመዘዋወር ሀገረ ስብከቱ በአጭር ጊዜ ውጤታማ የሆነ የአመራር እናየመንፈሳዊ አገልግሎት ሂደትን እንዲከተል አስችለዋል። 

 በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ የመጀመሪያ በሆነ መልኩ "መዝገበ ሕያዋንየተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ በማበልጸግ በሻሸመኔ እና ዙሪያው ባሉ ከተሞች የካህናት እናየምዕመናን ቆጠራ እንዲከናወን አድርገዋል። 

 ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከልን በመመስረት  ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በሚዲያው ዘርፍ ውጤታማለመሆን የሚያስችላትን አስተዋጽኦ የሚያደርግ ተቋም እውን አድርገዋል። 

 በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት የሰው ኃይል አስተዳደር ሲስተም በሀገረ ስብከቱ እንዲተገበርማድረጋቸው እና የሀገረ ስብከቱ አጠቃላይ እንቅስቃሴ ዕቅድ መር እንዲሆን ማስቻላቸው 

 የስብከተ ወንጌል አገልግሎትን በማጠናከር ኢአማንያን ወደ እውነተኛው የክርስቶስ በረትእንዲቀላቀሉ ማድረጋቸው። 

 በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለባለጉዳዮች የተሻለ መስተንግዶ ለመስጠት ለመጀመሪያ ጊዜ የቀጠሮመያዣ እያ የጉዳይ መከታተከያ ( Case Management System ) በማበልጸግ የሚታየውን ውስብስብችግር ለመፍታት በብፁዕነታቸው አማካይነት ጥረት እየተደረገ ይገኛል። 

 በዚሁ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአድባራት እና ገዳማትን የመሬት አጠቃቀም ዕቅድ መርለማድረግ እና ወቅቱን የተከተለ የመሬት አያያዝ እንዲኖር ለማድረግ የመሬት አስተዳደር ሲስተምበባለሙያዎች እንዲዘጋጅ በማድረግ ወደ ትግበራ እንዲገባ አድርገዋል። 

 በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር ለሚገኙ የክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት /ቤቶች ግንባታ ለማድረግከከተማ አስተዳደሩ ለሁለት ክፍላተ ከተሞች መስሪያ በከተማው መካከል ላይ 3,500 ካሬ ሜትር በላይመሬት እንዲሰጥ በማድረግ ትልቅ አሻራ ጥለዋል።

7. ፕሮጀክቶች እና ተቋማት 

 2013 - እስከ አሁን የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል መሥራች  የቦርድ ሰብሳቢ እና የበላይ ጠባቂ 

 2014 - እስከ አሁን የኢቲ አርት ሚዲያ የበላይ ጠባቂ 

 ከጥቅምት 2015 - ግንቦት 2017 . የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰብሳቢ